Show Bookstore Categories

Yane Lega Eyalen (ያኔ ለጋ እያለን)

Yane Lega Eyalen (ያኔ ለጋ እያለን)

ByDr. Samson Hanka

Usually printed in 3 - 5 business days
ይህ መጽሀፍ በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከ 1983 አም መጀመሪያ  እስከ 1988 አም መጨረሻ በጅማ ጤና ሳይንስ ኢንስቲቲዩት (ጅጤሳ) የህክምና ትምህርት ቤት እያለሁ በእለት ማስታወሻዬ የከተብኳቸውን፤ በኋላም ከግንቦት 2012 አም እስከ ነሐሴ 2014 አም በፌስቡክ ገጼ ላይ አኑሪያቸው የነበሩትን በርካታ የግል ማስተወሻዎችና  ወጎች አንድ ላይ በመጠረዝ የተዘጋጀ መጽሀፍ ነው። ማስታወሻዎቹ በህክምና ትምህርትቤት ውስጥ በመማር ሂደት የነበሩ የስሜት ውጣ ውረዶችና ሌሎችም ሁኔታዎች በአመዛኙ ፈገግታን በሚያጭር መልኩ የተዘገቡበት ነው። በ 1983 አም ኢትዮጵያን ያስተዳድር የነበረው የደርግ መንግስት ከትግራይ አማጺያን (ህወሀት) ጋር ያካሂድ ለነበረው ጦርነት መላው የኢትዮጵያ ኮሌጅና ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በውትድርና እንዲሰለጥኑ በተወሰነው መስረት ወደ ብላቴ ማሰልጠኛ ጣቢያ ከተጋዙት በርካታ ተማሪዎች ውስጥ አንዱ ስለነበርኩ የብላቴ ዘመቻ ታሪኬና አስገራሚ አጋጣሚዎቼም በዚህ መጽሀፍ ውስጥ ተካተዋል። በዚህ መጽሐፍ ውስጥ የቀረበው ጽሑፍ ከዋናው ማስታወሻ መያዣ (አጀንዳ) ላይ ሙሉ በሙሉ የተገለበጠ ሳይሆን መሠረተ ሐሳቡ ሳይዛነፍ፣ ስነ ጽሑፋዊ ውበት እንዲኖረው የአርትኦት ሥራ ተሰርቶለት የተዘጋጀ ነው። ከዋናው ማስታወሻ ላይ ከተውጣጡት በተጨማሪ አሁን ላይ ሆኜ በምልሰት የጻፍኳቸውም ተካተዋል። እነዚህ ግን በመጠን በጣም አናሳ ናቸው። ጽሑፉ  ፈገግታን ከማጫር በተጨማሪ አንባቢን ባለፉ ጊዜያትና ድርጊቶች ላይ አንተርሶ ወደ ግል ትዝታ ሊያስገስግስ ይችላል። አንባቢው ሀኪም ከሆነ ደግሞ ወደኋላ ሄዶ የራሱ የህክምና ትምህርት ቤት አጋጣሚዎች እንዲቃኝ ይረዳው ይሆናል። የዚህ ዘመን የህክምና ተማሪዎች፣ በተለይም  የጅማ ዩኒቨርሲቲ ሕክምና ተማሪዎች ምናልባት ይህንን ጽሑፍ የማንበብ እድል ከገጠማቸው ከሰላሳ ዓመት በፊት በኢትዮጵያ ስለነበረው የህክምና ትምህርት አሰጣጥ መጠነኛ ግንዛቤ ሊሰጣቸው ይችላል። ማስታወሻው ባጠቃላይ በኢትዮጵያ በ1980ዎቹ የነበረውን የህክምና ተማሪዎች ህይወት እንዲሁም የኢትዮጵያን ሁኔታ በከፊል ስለሚያሳይ ታሪካዊ ፋይዳም አለው። መልካም ንባብ። ዶ/ር ሳምሶን ኃይሌ ኃንቃ

Details

Publication Date
Jun 24, 2023
Language
Amharic
ISBN
9781312416529
Category
Biographies & Memoirs
Copyright
All Rights Reserved - Standard Copyright License
Contributors
By (author): Dr. Samson Hanka

Specifications

Pages
200
Binding Type
Paperback Perfect Bound
Interior Color
Black & White
Dimensions
A5 (5.83 x 8.27 in / 148 x 210 mm)

Ratings & Reviews